ሱፐርቪዥን
የከንቲባ ፅህፈት ቤት ሱፐርቪዥን ቡድን በአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በመገኝት የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም ላይ ምልከታ አደረገ ::
መስከረም 28/2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ
****
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከአዲስ አበባ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ለመጡ የሱፐርቪዥን አባላት የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም ሁኔታውን አስመልክቶ በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን ሪፖርት አቅርቦ ውይይት ተካሂዷል ::
የሱፐርቪዥን አባላትም በስድስት ክ/ከተሞችና በ12 የወረዳ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ፅህፈት ቤቶች ላይ ሱፐር
ቪዥን እንዳደረጉ ገልፀው ከታች የሚታዩት ችግሮች የሰው ሃይል እጥረት፣ የመልካም አስተዳደርና የመሳሰሉ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በዝግጅት ምዕራፍ ባደረጉት ምልከታ ቢሮው በተሻለ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ መሆኑን አስተያየት ሰጥተዋል።