ቢሮው ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች "በሰላም ዕሴት ግንባታ የወጣቶች ሚና"በሚል መሪቃል ስልጠና ሰጠ።
ቢሮው ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች "በሰላም ዕሴት ግንባታ የወጣቶች ሚና"በሚል መሪቃል ስልጠና ሰጠ።
ጥቅምት 01/ 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
*** ***
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የሰላም ዕሴትና የሃይማኖት ጉዳዮች ዘርፍ "በሰላም ዕሴት ግንባታ የወጣቶች ሚና"በሚል መሪቃል ከ11ዱ ክ/ከተማ የተወጣጡ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች ስልጠና ሰጥቶዋል ።
መድረኩ ላይ በመገኘት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ያቀረቡት የዘርፉ ባለሙያ አቶ ኤልያስ ቀጄላ ፦ የሰላም ምንነት፣ የሰላም ግንባታ አተያየቶች፣ ሰላምና ወጣትነት፣ በሰላም ግንባታ የወጣቶች ሚና በሚሉ ርዕሶች ላይ ስፋ ያለ ማብራርያ ሰጥተዋል ::
የሰላም ዕሴት ግንባታ የረጅም ጊዜ ሂደትን የሚጠይቅና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን የሚያካትት መሆኑን ጠቅሰዉ ወጣቶች ሁሉን አቀፍ አቅማቸዉን ለሰላም ግንባታ በማዋል ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ አስተዋፅኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል::
መድረኩን የመሩት የዘርፉ ዳይረክቶሬት ዳይረክተር አቶ ተመስገን እጅጉ ሲሆኑ የተለያዩ የአደባባይ በዓላት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብረው ማለፋ ቸው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ሚና ስላለበት ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል ::
በተለይም ወጣቶች ደግሞ የህብረተሰቡ የማይነጥፍ ክንድ በመሆናቸው ግጭት ከመከሰቱ በፊት በባሕላዊና ዘመናዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች በመጠቀምና በመወያየት ለሰላሙ ዘብ መቆም ይኖርበታል ብለዋል።