የአዲስ አበባ ከተማ እና የሸገር ከተማ አስተዳደር በፀጥታ ፣ በወንጀል መከላከልና የህግ የበላይነት የማረጋገጥ ስራ በጋራ ለመስራት የውል ስምምነት ተፈራረሙ
የአዲስ አበባ ከተማ እና የሸገር ከተማ አስተዳደር በፀጥታ ፣ በወንጀል መከላከልና የህግ የበላይነት የማረጋገጥ ስራ በጋራ ለመስራት የውል ስምምነት ተፈራረሙ።
ሁለቱም ከተማ አስተዳደሮች ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት በተለየ መልኩ ጥረት ማድረግና ማስጠበቅ ፣ የሰላም ሰራዊት አደረጃጀቶችን በሎጀስቲክና በተለያዩ ስልጠናዎች መደገፍ ፣ የድጋፍና ክትትል ስራን ማጠናከር ፣ ጨለማን ተገን አድርጎ የሚሰሩ ወንጀልንና የስጋት ቦታዎችን በመለየት ህብረተሰቡ መረጃ እንዲሰጥና ለፀጥታ ሀይሉ አቅም እንዲሆን ማስቻል ፣ የፀረ ሽብርተኞችን አሸንቅስቃሴዎችን ተከታትሎ ማጥፋት፣ማህበረሰቡ ከአደጋ ስጋቶች እራሳቸውን እንዲጠብቁ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ላይ ትኩረት ያደረገ የጋራ የውል ስምምነት የከተሞቹ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተፈራርመዋል።
ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም
ሰላም ከሁሉም... በሁሉም... ለሁሉም!
📞 የፀጥታ መረጃ ጥቆማ ለመስጠት፦ 8882 ነፃ የስልክ መስመርን ይጠቀሙ።
https://linktr.ee/qr/e5702bda-a953-4926-8253-c3bd2f978c7977157