የ1ኛ ሩብ ዓመት ግምገማ
የቢሮው የህዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ከተለያዩ አደረጃጀቶች ጋር የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድን ገመገመ።
ጥቅምት 14/ 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
* *
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የህዝብ አደረጃጀት ዘርፍ በጋራ አብረው ከተለያዩ የህዝብ አደረጃጀቶች ጋር የ2017 ዓ.ም የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድን ገምግሞአል::
የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ በ ዚህን ወቅት እንደተናገሩት ቢሮው 11 ሺህ ወጣት የሰላም ሰራዊት አባአላት አሰልጥኖ ከነባር የሰላም ሰራዊት ጋር እንዲቀላቀሉ ማድረጉን ፣ በከተማዋ የጫኝ እና አዉራጆችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናግረዋል ።
ከአንድ ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የህብረሰብ ክፍሎችን በሰላም ዙሪያ ማወያየቱ በሩብ አመቱ ከነበሩ አንኳር ተግባራት መካከል መሆናቸዉን አንስተዋል ።
በተለይ ህብረተሰቡን ያማከሉ በርካታ ተግባራት በመተግበራቸዉ የአዲስ አበባን ሰላም ማጠናከር ችሏልም ብለዋል ።
የበጀት አመቱ ሩብ አመት በከተማዋ በርካታ የአደባባይ በአላትንና አለም አቀፋዊ ጉባኤዎችን ያለምንም የጸጥታ ችግር ያከናወነችበት እንደነበርም አንስተዋል ምክትል ቢሮ ሃላፊዉ ።
ለዚህ ስኬት የህብረተሰብ አደረጃጀቶች የአንበሳዉን ድርሻ ተወጥተዋል ብለዋል ።