ፖሊስ ኮሚሽን ማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት የ ስራ ኃላፊዎችና አባላት ጋር የተደረጌ ውይይት
በየደረጃዉ ከሚገኙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት የ ስራ ኃላፊዎችና አባላት ጋር ውይይት ተካሄደ ።
ጥቅምት 14/ 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
****
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የህዝብ አደረጃጀት ዘርፍ
በየደረጃዉ ከሚገኙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት የ ስራ ኃላፊዎችና አባላት ጋር ውይይት ተደርጎዋል::
በ2017ዓ.ም በተያዘው ዕቅድ መሰረት ለአስራ አንድ ሺ የሰላም ሰራዊት አባላት የንድፈ ሀሳብና የመስክ ወታደራዊ ስልጠና በአንደኛ ሩብ ዓመት የተሰጠ ሲሆን በስልጠናው ወቅት የነበሩ ጠንካራ ጎኖች እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮችን በተመለከተ አቶ አብርሃም እንግዳወርቅ የዘርፉ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ማብራሪያ ተሰጥቶዋል ።
የሰላም ሰራዊቱ ስልጠና አቅምን የፈጠረ እንደሆነ ሁሉ የስምሪት ስራውን አጠና ክሮ በማስቀጠል የሚታዩ አንዳንድ ክፍተቶችን ማረም እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ማህበረሰብ አቀፍ ዕቅድና ጥናት ሀላፊ ም/ኮማንደር ታዲዎስ አክሊሉ ገልጸዋል።
መድረኩን የመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ም/ቢሮ ሀላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ እንደገለፁት የሰላም ዋስትናን ለማረጋገጥ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ሀይሉ ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመጠቆም በየግዜው ህብረተሰቡን በየአካባቢው በማወያየት የሰላም ባለቤት በማድረግና አጋዥ እንዲሆኑ በማስቻል ወንጀሎችን ለ መቀነስ የሚደረገው ጥረትን በማድነቅ አምስግነው በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ብለዋል።