Events

Events የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

image description
Start Date icon
End Date icon
Location ከተማ አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ

ፕሬስ ሪሊዝ

ህዳር 30/2017 ዓ.ም

******

የአዲስ አአበባ ሰላምና ፀጥታአስተዳደር ቢሮ ከተማ አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ ሊካሄድ ነው ።

" ሀገር ወዳድነትና የሀገረ መንግስት ግንባታ" በሚል ርዕስ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ የግንባር ቀደም ሚናቸውን ይወጡ ዘንድ የተዘጋጀ ኮንፈረንስ መሆኑን የቢሮዉ ም /ኃላፊ አቶ ተሰፋዬ ጫኔ ገልፀዋል።

እንደምክትል ቢሮ ሃላፊዉ ገለፃ የሰላም ኮንፈረንሱ በ 119 ወረዳዎች ነገ ማለትም ማክሰኞ እና በ 11ዱም ክ/ ከተሞች ደግሞ ሀሙስ በአንድ ቀን ይካሄዳል ብለዋል።

የኮንፈረንሱን ተሳታፊዎች በተመለከተ

በየወረዳው 500 እና በየክፍለ ከተማው 1000 ተሳታፊዎች የሚሳተፉ ሲሆን በጠቅላላዉ እንደ ከተማ ከ80,000 በላይ ህዝብ ይሳተፋል ብለዋል።

ኮንፈረንሱን ከነገ ታህሳስ 1/2017 ዓ. ም ጀምሮ ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸዉን ም/ቢሮ ኃላፊዉ ተናግረዋል ።