Events

Events የቅርብ ጊዜ ሁነቶች

image description
Start Date icon
End Date icon
Location 11ክፍለ ከተማ

4ኛ ኮርስ አዲስ ምልምል የሰላም ሰራዊት ስልጠና ሊጀመር ነው

ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም (አዲስ አበባ)

******

የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ስተዳደር ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት 4ኛ ኮርስ አዲስ ምልምል የሰላም ሰራዊት ስልጠና ሊጀመር ነው::

ስልጠናው ከነገ ሚያዝያ 16 ቀን ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ለአስር ተከታታይ ቀናት የሚካሄድ ሲሆን የንድፈ ሃሳብና የመስክ ወታደራዊ ስልጠና እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ም/ል ኃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ ገልፀዋል፡፡

ም/ቢሮ ኃላፊው አክለውም የሰላም ሰራዊት አባላት ምልመላ፤ስልጠናና ስምሪት ህብረተሰቡን የሰላም ባለቤት የማድረጊያ አንዱ መንገድ መሆኑን ጠቅሰው በያዝነው በጀት ዓመት ስልጠና ሲሰጥ ይህ 3ኛው ዙር መሆኑን ተናግረው በዚህ ዙር አስራ አንድ ሺ ሰልጣኞች እንደሚከታተሉ ገልፀዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም ለክፍለ ከተማ አስተበባሪዎችና ድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎች ኦረንቴሽን መሰጠቱን ጨምረው ገልፀዋል፡፡